በኢትዮጵያ አፋር ክልል ውስጥ የሚገኘው የሃይሊ ጉቢ እሳተ ገሞራ ከ10,000 እስከ 12,000 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ እሁድ እለት (ህዳር 13/14 ቀን 2018 ዓ.ም. አከባቢ) ተቀስቅሷል። ይህ ክስተት የሆሎሴን ዘመን ከተጀመረ ወዲህ የመጀመሪያው የተመዘገበ ፍንዳታ እንዲሆን አድርጎታል።
የእሳተ ገሞራው አመድ ደመና እስከ 14 ኪሎ ሜትር ከፍታ ላይ በመድረስ በቀይ ባህር አሻግሮ ወደ የመንና ኦማን ተሰራጭቷል።
በአቅራቢያው የሚገኘው የአፍዴራ መንደር ሙሉ በሙሉ በአቧራ ተሸፍኗል። በኤርታ አሌ እና በአፍዴራ ከተማ አካባቢ መጠነኛ የሆነ መንቀጥቀጥ እንደተከሰተ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ሃይሊ ጉቢ የሚገኘው ከኤርታ አሌ እሳተ ገሞራ በደቡብ ምስራቅ በ15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው። ፍንዳታው ከፍተኛ የሰልፈር ዳይኦክሳይድ እና የመስታወት ቅንጣቶችን የያዘ ደመና ያስከተለ ሲሆን፣ በሰሜናዊ አረቢያ ባህር ላይ ተዘርግቶ ወደ ህንድ እና ሰሜናዊ ፓኪስታን አቅጣጫ ነው የተጓዘው።
አመዱ በህንድ ውስጥ ጉጃራት፣ ራጃስታን እና ዴሊ ባሉ ክልሎች ላይ "ተንሳፏል።

አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ