ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

የኮንሶ ፋሌክ ከዝሆን ጥርስ በክብ ቅርጽ የተሰራ ነው።

 





ምድሯ ኢትዮጵያ ናት። እያንዳንዱ የየራሱ ባህል ፥ እምነት እና አምላክ ይዟል። ከሚያምኑት እምነትም የተነሳ እያንዳንዳቸው በዙሪያቸው ስላለው ዓለም እና ስለ ሐይቆች አፈጣጠር ፥ ስለ መጨረሻው ሕልፈተ ሰማይ ወምድርም የራሱ የሆነ ግንዛቤ አለው። የሚታየው ምስል ፋሌክ ነው። በግብፅ እና በኢትዮጵያ መካከል ትስስር መኖሩን አመላካች ነው። ግብፃውያን አማልክቶች ከፑንት አገር እንደመጡ ያምኑ ነበር። የፑንት ምድር ደግሞ የዛሬዋ ኢትዮጵያ ናት። በግብፅ ንግሥት ሃትሼፕሱት ቤተ መቅደስ ውስጥ አንድ ትልቅ ፎቶግራፍ ወደ ፑንት የአማልክት መገኛ ምድር የተደረገውን ጉዞ ይናገራል። ከ 3500 ዓመታት በፊት የፑንት ምድር ሀብታም ግዛት ስለነበረች ከንግድ ተልዕኮ ጋር የተጣመረ ምሥጢራዊ ጉዞ ይካሄድበት ነበር። የግብፅ ጽሑፎች እንደሚናገሩት ከሆነ " ወደ አማልክት ምድር ዳርቻ ለመድረስ በቀይ ባህር ላይ ለሁለት ወራት ያህል በመርከብ ይጓዙ እንደ ነበር ያወሳሉ።


ከ 3500 ዓመታት በፊት የግብጻዊያን ጉዞ ምናልባት ምድራችን ሙሉ በሙሉ በቀይ ባህር ስለተሸፈነች በጣም ርቀው እንደ መጡ ያሳያል።
በጉዟቸው መጨረሻ ላይ ግብፃውያን በስምጥ ሸለቆ ዙሪያ ያሉትን ኮረብታዎች እና የድንጋይ ምሰሶ ግዛቶች ደርሰውባቸው ሊሆን ይችላል። ምን አልባት ከአፍሪካ ውድ የሆኑ ሸቀጣሸቀጦች የተወሰደበት ምስጢራዊ መንገድ ሊሆን ይችላል። ወደ ግብፅ የሚገቡ ውድ የንግድ ዕቃዎች የአማልክትን ሀብት ሊያብራራ ይችላል። ምናልባት ሐውልቶቹ ለአማልክት ምስጋና ይሆን ዘንድ በጥንት ሰዎች የተገነቡ ይመስላል። ከዚያም የሐይቆች መድረቅ እና የግብፅ ኢምፓየር ውድቀትን ተከትሎ የድንጋይ ምሰሶ ጠራቢዎች በምድሪቱ ቀሩ። ጥበባቸውም።

ከዘሮቻቸው የቀሩትም ጥቂት ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ እና ወደ ደቡብ ተሰደዱ። የኮንሶው ገበሬዎች ዘላኖች ያልሆኑ የእጅ ባለሞያዎች ናቸው። በከብቶች በማረስ ማሽላ ያመርታሉ። ኮንሶ እና ቦረና የክልሉ ብቸኛ ነዋሪዎች ናቸው። ከድንጋይ ቀረጺ ዘሮች የተረፉ። የመንደሩ ቤተመቅደስ በተከታታይ በቀብር ሥርዓቶች ያጌጠ ነው። ቅድመ አያቶቻቸውን ይወክላሉ።
እና አንዳንዶቹ ስልጣናቸው የሚገልጽ ፋሌክ አድርገዋል።

የኮንሶ ባለሙያዎች ባህላዊ ዋጋ ያለውን ፋሌክ በመስራት ዝነኛ ናቸው። አንጥረኛው የሚጀምረው ብረቶችን በማቅለጥ ነው። የኮንሶ ፋሌክ ውድ ነው። ከዝሆን ጥርስ በክብ ቅርጽ የተሰራ ነው።ቃሉ የመንደሩ አለቃ እና የባህሉ ጠባቂ ነው። ቅዱስ ፋሌክ አለው። በማሰሮ ውስጥ ያስቀመጠዋል። ጸሎቱን ወደ እሱ ያደርሳል። የጸሎቱን መልስ ከሰማይ ያገኘዋል። የመንደሩ ቃሉ ሰማይን ያምናል። ፋሌክ በሞቱ ሰዎች ከዛም አልፎ በፎችም ነፍስ ውስጥ የሚኖር የተቀደሰ ነው። እነሱን መግደል ወይም መብላት የከፋ ኃጢአት ነው። ፋሌክ ለአምልኮ ሥርዓት የተቀደሰ ነገር ነው።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

በዳልሆል ሳዶን ጂኦሎጂያዊ እንቅፋት፣ በታሪካዊ ውድቀት እና በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት የታጠረችው ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ የባህር መዳረሻ ለማግኘት የምታደርገው ትግል በጂኦሎጂያዊ እንቅፋት፣ በታሪካዊ ውድቀት እና በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት የታጠረ ነው።  ነገርን ከስሩ፥ ውኃን ከጥሩ ነው እና እንዬው።  ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ውስጥ ካሉት ዋና ዋና ሀገሮች አንዷ ብትሆንም፣ ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ ያለባህር በር መቆየቷ አገራዊ ደህንነቷን እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገቷን የሚገዳደር የዘመናት ችግር ሆኖ ቆይቷል። ይህ ታሪካዊ ፈተና፣ የጂኦሎጂያዊ ፍጥረት ሚስጥር ከሆነው  #ከዳልሆል_ሳዶን  ተፋሰስ እና ከአሁኑ የቀይ ባህር የኃይል ሚዛን ጋር የተሳሰረ ነው።  በዳልሆል_ሳዶን  ዙሪያ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል ታሪክ የተጀመረው በንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ሲሆን፣ በ1955 ዓ.ም. ነው። በ1991 ዓ.ም. ወደ 11,500 የሚጠጉ ሠራተኞች እና 81 የሚደርሱ የተለያዩ ዓይነት መርከቦች የነበሩት ሲሆን፣ በጊዜው በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ጠንካራ የባህር ኃይሎች አንዱ ነው። ኃይለ ሥላሴ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል ዩኒፎርም ለብሰው። ዋና መሥሪያ ቤቱና ዋና የሥልጠና ማዕከሉ ምጽዋ ውስጥ የነበረ ሲሆን፣ ሌሎች መሠረቶቹ ደግሞ  #አሰብ፣ #ዳህላክ_ደሴቶች እና #አስመራ  ውስጥ ነበሩ። በ1996 ዓ.ም. ኤርትራ ነፃነቷን ስትቀዳጅ፣ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ በመሆኗ የባህር ኃይሉ ተበተነ። መርከቦቹ በጅቡቲ እና በየመን ወደቦች ለጊዜው ከቆዩ በኋላ ተሸጡ። ፈረራሱ። ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያ ከ95% በላይ የንግድ እንቅስቃሴዋን በጅቡቲ ወደብ ላይ እንድታደርግ ተገደደች። የኢትዮጵያ ወደብ አልባነት መንስኤ የፖለቲካዊ ውሳኔ ቢሆንም፣ የቀይ ባህር ውኃ ወደ ዳንኪል በረሃ እንዳይፈስ የሚከለክለው ጂኦሎጂያዊ ምክንያት ደግሞ  የ...

ዳንኪል በረሃ በከፍተኛ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ተናወጠ

 አስቸኳይ ዜና፡ ዳንኪል በረሃ በከፍተኛ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ተናወጠ! 🗓️ ቀን፡ ህዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ⏱️ ሰዓት: ከቀኑ 4 ሰዓት አካባቢ በኢትዮጵያ አፋር ክልል ዳንኪል በረሃ ውስጥ ከፍተኛና አስደንጋጭ የሆነ የጂኦሎጂ እንቅስቃሴ ተመዝግቧል። የዓለም ዝነኛ ከሆነው እርታሌ እሳተ ገሞራ አጎራባች በሆነው አሊ ባጉ ተራራ ላይ፣ በተለይም በሐይሊ ጉቢ እና በአማይቶሌ መካከል፣ ኃይለኛ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ መከሰቱ ተረጋግጧል። ይህ ፍንዳታ ከወትሮው የተለየና እጅግ ከፍተኛ ኃይል ያለው መሆኑን የሚያመላክቱ ሁለት አስደንጋጭ ክስተቶች ተስተውለውበታል።  የእሳተ ገሞራው ወፍራም አመድና ጋዝ (ጢስ) በሰዓት ውስጥ በብዙ ሺህ ሜትሮች ተተኩሶ እስከ ሩቅ የትግራይ ተራራዎች ድረስ መታየቱ ተዘግቧል። ይህ የአመድ ልቀት ፍንዳታ (Explosive) እንደነበር ተስተውላል።   አንዳንድ የአይን እማኞች "የእሳተ ገሞራ መብረቅ" (Volcanic Lightnings) የሚባለውን ያልተለመደ ክስተት ተመልክተዋል። ይህ የሚከሰተው በጢሱ ደመና ውስጥ ያሉት ቅንጣቶች በከፍተኛ ፍጥነት በመፋተግ ስታቲክ ኤሌክትሪክ ሲፈጥሩ ነው። ይህም የፍንዳታው ኃይል እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው። ከእርታሌ ሰንሰለት አንጻር ይህ ክስተት ዳንኪል አካባቢ ላይ የጂኦሎጂ ሁኔታ መፋጠኑን የሚያሳይ ነው።  አሊ ባጉ፣ ሐይሊ ጉቢ እና አማይቶሌ የእርታሌ የእሳተ ገሞራ ሰንሰለት (Erta Ale Volcanic Range) አካል ሲሆኑ ፍንዳታው የተከሰተው በመደበኛው የእርታሌ ጉድጓድ ሳይሆን በአዲስ ስምጥ መስመር (Fissure Eruption) ላይ ነው። ይህ የሚያመለክተው የምድር ንጣፎች (የአፍሪካ እና ዐረብ ሰሌዳዎች) መለያየት እየጨመረ መምጣቱን ነው። የእርታሌ ማግማ ዝቅተ...

የዳንኪል በረሃ ሚስጥር፡ ምድር አዲስ ውቅያኖስ የምትወልድበት ስምጥ

ዳንኪል በረሃ በኢትዮጵያ ሰሜን ምሥራቅ የሚገኝ ሲሆን፣ ወደ ኤርትራና ጅቡቲ ይዘልቃል። በአለም ጂኦሎጂ ውስጥ ያለው ዋነኛው ጠቀሜታ የሚመጣው ከ አፋር ሶስት ማዕዘን (Afar Triangle) አቀማመጥ ነው። ይህ ሶስት ማዕዘን የሚባለው አካባቢ ሦስት ግዙፍ የቴክቶኒክ ሳህኖች የሚገናኙበትና እርስ በእርስ የሚራራቁበት ወሰን ነው፡-  * የአረቢያ ሳህን (Arabian Plate)  * የኑቢያን ሳህን (Nubian Plate - የአፍሪካ ዋና ክፍል)  * የሶማሊያን ሳህን (Somalian Plate) እነዚህ ሳህኖች ቀስ በቀስ በመራራቃቸው ምክንያት የሚፈጠረው የመወጠር ኃይል (Tensional Stress) የምድርን ቅርፊት እየሰነጠቀውና እያሳሳው ይገኛል። ይህ ሂደት ስምጥ ሸለቆ (Rift Valley) እንዲፈጠር አድርጓል፤ ዳንኪል በረሃ የዚህ ስምጥ ሰሜናዊ ጫፍ ነው። ይህ የመለያየት ሂደት አዲስ ውቅያኖስ ለመፍጠር ዝግጅት እያደረገ ነው። ኤርታሌ በዳንኪል በረሃ ውስጥ ከሚገኙት እጅግ ዝነኛ እና ንቁ የእሳተ ገሞራዎች አንዱ ሲሆን፣ በጎሳው ቋንቋ "የሚያጨስ ተራራ" ማለት ነው። የሺልድ እሳተ ገሞራ እና የእሳት ሐይቅ ኤርታሌ መሰረታዊ የሺልድ እሳተ ገሞራ (Shield Volcano) ዓይነት ነው። እጅግ ዝነኛ የሚያደርገው ደግሞ የእሳት ሐይቅ (Lava Lake) በጫፉ ላይ መኖሩ ነው።  * የእሳት ሐይቅ፡ ኤርታሌ በዓለም ላይ ካሉ በጣም ጥቂት የእሳት ሐይቅ ካላቸው እሳተ ገሞራዎች አንዱ ነው። ይህ ሐይቅ ቀጣይነት ባለው መልኩ የቀለጠው እሳተ ጎመራ የሚንተከተክበት ጉድጓድ ነው። ላቫው ለበርካታ አስርት ዓመታት ያለምንም መቆራረጥ በንቃት ሲንቀሳቀስ ቆይቷል።  * አካባቢ: በአብዛኛው ጥቁር ጠጣር ላቫ የተሸፈነ ሲሆን፣ የእሳተ ገሞራው ንቁ እንቅስቃሴ...